Saturday, 29 June 2013

ወይዘሮ አዜብ እና ”ለመንግስት ተመላሽ ሊደረግ የነበረ ሰባ ሚሊዮን ብር (70.000.000)


qw
ስብሃት ነጋ …ህዝብን የሚያደነቁሩትን እነበረከትንና የጋሪ ፈረስ የሆኑት ሃ/ማሪያምን እርቃናቸውን አስቀሩ::
ሽማግሌውን በቅርብ የሚያውቋቸው የፓርቲው ሰዎች « ስብሃት ከበረሃ ጀምሮ በቀለኛ ነው። ጥርሱ ውስጥ የገባን ሰው ካላስወገደ እንቅልፍ አይወስደውም፤ ብዙ ሰው አጥፍቶዋል። አሁንም አዜብን እግር በእግር የሚከታተለው ለዚሁ ነው» ይላሉ።
አባተ ኪሾ ከደቡብ ባጀት ተመላሽ የሆነ ሰባ ሚሊዮን ብር (70.000.000) ለመንግስት ተመላሽ ሊያደርጉ ሲሉ …« ወዲህ በል..የምን መንግስት ነው?» በማለት ተቀብለው ኪሳቸው የከተቱት አዜብ መሆናቸውን አባተ ፍ/ቤት ጭምር ያጋለጡት ነው። ስብሃት ነጋና መለስ ዜናዊ ደግሞ ታምራት ላይኔ በውሸት እንዲመሰክር አምስት ጊዜ አግባብተውት እንቢ ሲል ከማስደብደባቸው በተጨማሪ ሌላ ክስ እንዲመሰረትበት አድርገዋል። አቃቤ ሕግ የነበረው ዮሃንስ ወ/ገብርኤል የነስብሃትን የውሸት ክስ ተቀብዬ ተግባራዊ አላደርግም፤ ህሊናዬ አይቀበለውም .. በማለቱ ብቻ ለአምስት አመት እንዲታሰር አላደረጋችሁም?…ብዙ ማስረጃና መረጃ መደርደር ይቻላል።..
ሽማግሌው ስብሃት ነጋ ከጥቂት ቀናት በፊት በሰጡት ቃለ-ምልልስ አስበውት ይሁን ሳያስቡት “እውነት” አምልጧቸዋል። አጥብቀው ያነሷቸው የሙስና ጉዳዮች ራሱን የቻለ « አላማና ግብ » አላቸው። የመጀመሪያው በፓርቲያቸው ውስጥ ያለው ክፍፍል (የጥቅም) እንደተዳፈነ እሳት ውስጥ ለውስጥ እየተብላላ መሆኑን በግልፅ ያሳያል። ከተናገሩት የሚከተለውን እንመልከት፤ « .በጤናማ ሁኔታ የሚገኙ ሰዎችን እንቆርጣለን፣ እናስራለን ወዘተ እያሉ ሲያስፈራሩ የነበሩ የፖለቲካ፣ የመንግስት ሰዎች ነን የሚሉ የፀጥታና የስነ አእምሮ ሁከት ፈጥረዋል። መቶ ሚሊዮን የሰረቁና ያስዘረፉ፣ 10ሺህ ብር የሰረቀውን ሲያገላብጡት ያታያሉ። » ብለዋል። « እንቆርጣለን » ያሉት መለስ ዜናዊ ናቸው፤ መለስ በአደባባይ ይህን ከመናገር አልፈው ሲያስፈራሩም እንደነበር እናስታውሳለን። መለስ ያንን ያሉት በ10ሺዎች የሚገመት ቡና ከመጋዘን ጠፋ በተባለበት ወቅት ነው። ያንን ቡና የሰረቁትና ባህር ማዶ ሸጠው ገንዙቡን ኪሳቸው የከተቱት አዜብ መሆናቸውን ከዚህ ቀደም ምንጭ ተጠቅሶ ይፋ ተደርጓል። እናም ስብሃት “መቶ ሚሊዮን የሰረቁ..» ያሉት አዜብ መስፍንን ሲሆን፣ « ያስዘረፉ» ያሉት ደግሞ ባለቤታቸው አቶ መለስን ነው። « 10ሺህ የሰረቁ..» የተባሉት በቅርቡ የታሰሩት የጉምሩክ ሰዎችን ሲሆን..እነዚህን በንፅፅር ያስቀመጡት የአዜብ (ተላላኪዎች) ስርቆት መጠነሰፊ መሆኑን ለማመላከት ነው። ስብሃት እስካሁን አድፍጠው ቆይተው በዚህ ሰሞን ይህን መናገራቸው ..«አዜብ የከተማዋ ም/ል ከንቲባ ይሆናሉ» የሚባለውን በመስማታቸው ሆን ብለው ያደረጉት ነው፥ ይላሉ ታዛቢዎች።
« ሙስና ከተነሳ ስብሃትም እስከአንገቱ ተነክሮበታል። በገርጂና ሳር ቤት የሚገኘው በአሜሪካ በሚኖሩ ስጋ ዘመዶቹ ስም እንዲሁም በቀድሞ የአየር ሃይል ጄ/ል ሰሎሞን ስም የሚንቀሳቀስ ግን የስብሃት የግል ንብረት መሆኑን የማይታወቅ መስሎት ነው?….ጎንደር -ሑመራ ያለው የሰሊጥ እርሻ የስብሃት አይደለም?…በ10ሚሊዮን ብር በሚገመት በመቀሌ (አፓርታይድ መንደር) ስብሃት ዘመናዊ ቪላ እንደሚገነባ አይታወቅም ብሎ ይሆን?…» ሲሉ እነዚህ ወገኖች የስብሃትን ሙስና በከፊል ይጠቅሳሉ።
ስብሃት በዚህ አላበቁም፤ « ..እስካሁን ከፍተኛ ሙሰኞች ትንሹን ሙሰኛ ከሰው አሳስረው ያስፈርዱና ያሰቃዩ ነበር ይባላል። ከፍተኛ ሙሰኞች ከመርማሪው ጀምረው አቃቤ ሕጉም ዳኛው፣ ምስክሩም ይቆጣጠራሉ። ትንሽ የሰረቀም ምንም ያልሰረቀም ሲሰቃዩና ሲያደኸዩ የነበሩም፤ አሉም ይባላል። ስልክ እየደወሉም ይፈርዱ ነበር ይባላል።» ብለው አረፉት ስብሃት። ትክክል ናቸው!! ዳኛ ብርቱካን ሚዴቅሳ « ይህን ካልፈረድሽ በመኪና ገጭተን ነው የምንገድልሽ » ተብላለች። ያውም ከቤተ መንግስት ተደውሎ።
አሁን ስብሃት ተናገሩት እንጂ…ህዝቡ ብሎ-ብሎ የታከተው ነገር ነው!! እነ እስክንድር፣መሃመድ አቡበከር፣ አንዷለም አራጌ፣ ርእዮት አለሙ….ወዘተ በርሶ ጓደኞች በስልክ ትእዛዝ የተፈረደባቸው ናቸው!!… «ፍትሃዊ ስርአትና መንግስት አለ..» እያሉ ህዝብን የሚያደነቁሩት እነበረከትና የጋሪ ፈረስ የሆኑት ሃ/ማሪያም እርቃናቸውን የሚያስቀር ነገር ነው በስብሃት የተቀመጠው።

Monday, 24 June 2013

የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት የኖርዌይ ቻፕተር በኦስሎ ከተማ የተሳካ ህዝባዊ ስብሰባ አደረገ


የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት የኖርዌይ ቻፕተር ጠቅላላ ህዝባዊ ስብሰባውን ሰኔ-15, 2005 
ዓ.ም (ጁን 22 ቀን 2013 ) ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች በተገኙበት ታሪካዊና 
ስኬታማ የሆነ ህዝባዊ ስብሰባ አደረገ። በእለቱም በተጋባዥ እንግድነት አቶ ሰለሺ ጥላሁን የሽግግር ምክር 
ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ ፣ ሚስተር አዳም ዊስ በአውሮፓ የግለሰብ መብት አማካሪ ማእከል ዋና ዳይሬክተር 
ደራሲና ገጣሚ አቶ አበራ ለማ እንዲሁም በኖርዌይ የሽግግር ምክር ቤት የዲፕሎማቲክ ተጠሪ ዶ/ር 
ግሩም ዘለቀ ተገኝተው ነበር። 
ፕሮግራሙ የተጀመረው በ ዶ/ር ግሩም ዘለቀ የመክፈቻ ንግግር ሲሆን ፣ ስደተኞችንና ዲፕሎማሲን 
አስመልክቶ አጭር ገለጻ በማድረግና ተጋባዥ እንግዶችን በማስተዋወቅ ስብሰባው ክፍት እንደሆነና 
ታዳሚዎችም ማብራራዎችን ተከትሎ ጥያቄዎቻቸውን እና አስተያየቶቻቸውን ማቅረብ እንደሚችሉ 
አስገንዝበዋል።
 በመቀጠልም ሚስተር አዳም ዊስ ስለ ጥገኝነትና ተከታትለው ስለሚመጡ የመብት 
ጥያቄዎች ማብራሪያ አድርገው ኢትዮጲያውያን በኖርዌይ ተደራጅተው ለሰብአዊ መብት ፍርድ ቤት 
ያስገቡትን የጥገኝነት ጥያቄ ክስ በተመለከተም ያሉበትን ሁኔታ አስረድተዋል። ከተሳታፊዎችም ለተነሱ 
ጥያቄዎች አንድ በ አንድ መልስ ሰጥተዋል።
 ደራሲ አቶ አበራ ለማ ከስራዎቻችው መካከል ጥቂቱን ለታዳሚው ያቀረቡ ሲሆን ፣ ኢትዮጵያና 
የኢትዮጵያዊነትን ስሜት የሚቀሰቅሱ ወቅታዊ ግጥሞች በአማርኛና በኖርዌጅያን ቋንቋ አሰምተዋል። 
በመቀጠልም፤ የሽግግር ምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ፤ አቶ ሰለሺ ጥላሁን ስለ ሽግግር ምክር ቤቱ ምንነት፤
አላማውንና የወደፊት አቅጣጫውን አስመልክቶ በሚከተሉት አብይ እርሶች ላይ ሰፊ ገለፃ አድርገዋል። 
  • የግፍ አገዛዝን ለማስወገድ ያሉን 5 አማራጮች
  • የምክር ቤቱ የቅድመ ምስረታ ሂደት
  • የምክር ቤቱ የምስረታ ጉባኤ
  • የምክር ቤቱ ድህረ ምስረታ እንቅስቃሴዎች
  • ለወገኖቻችን በአለም ዙርያ እንቁም
  • ስለሽግግር አሁን መነጋገር ለምን አስፈለገ?
  • ስርአቱን ሰለማስወገድና በሁሉ ሁሉ አቀፍ የሽግግር መንግስት ስለመተካት በዋሽንግተን ዲሲ ከጁላይ 2-5/ 2013 ስለሚደረግ ሁሉን አቀፍ የምክክር ጉባኤ።
ከማብራሪያዎች በሗላ ሰፋ ያለ የጥያቄና መልስ ፕሮግራም የነበረ ሲሆን፣ ከታዳሚዎች ለቀረቡ 
ጥያቄዎችም፤ አቶ ሰለሺ ጥላሁን አንድ በአንድ መልስ ሰጥተዋል። በቀረቡት ማብራሪያዎች የተደሰቱ 
34 አዲስ አባላቶች የአባልነት ፎርም በመሙላት የኖርዌይ ቻፕተርን ተቀላቅለዋል። 
ህዝባዊው ስብሰባ ከተጠናቀቀ በሗላ አቶ ስለሺ ጥላሁን ከነባርና አዳዲስ አባለቶች ጋር አጠር ያለ 
ስብሰባ በማድረግና በህገ ደንቡ መሰረት ያባላትን መብትና ግዴታ ማበራሪያ በመስጠት፤ ቻፕተሩን 
የማጠናከርና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ አዳዲስ የኮሚቴ አመራር አባላት ምርጫ የተካሄደ ሲሆን፣ 
በምርጫውም የሚከተሉትን አስራ አምስት አስተባባሪ አባላቶችን አፅድቛል፤ 

አቶ እንግዱ ወርቁ ፣ አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ ፣ አቶ አዲስ ማሞ፣ አቶ ንጉስ ቱሉ፣ ወ/ሪት ሄለን ደሬሳ ፣ አቶ 
ናኦድ ከበደ፣ ወ/ሪት ፍቅርተ ነጋሳ፣ አቶ አርጋው ከበደ፣ ዶ/ር ግሩም ዘለቀ፣ አቶ ዮሃንስ ልኡል፣ አቶ 
ስብሃት አማረ፣ ወ/ሮ እመቤት ካሳሁን ፣ ወ/ሪት መሰለች ቸርነት፣አቶ አንዋር ሃሩን እና ወ/ሪት ሃና 
ሲሆኑ ።
 
በመጨረሻም፤ በሊቀመንበርነት ዶ/ር ግሩም ዘለቀን፣ በ ዋና ፀሀፊነት አቶ ናኦድ ከበደን፣ በገንዘብ 
ያዥነት ወ/ሪት ሄለን ደሬሳን በመምረጥ ታርካዊው የኖርዌይ ቻፕተር ስብሰባ በስኬት ተጠናቛል። 
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር
የኖርዌይ ቻፕተር!

Sunday, 23 June 2013

Dr. Berhanu Responds Re: Broadcast Of His “Pvt’ Voice Records”

June 22, 2013 Source: De Birhan
with ESAT Radio today, Dr. Berhanu nega
Dr. Berhanu Nega, associate professor of Economics at Bucknell University and Chairman of the opposition movement, Ginbot 7, has responded to  recent reports by some websites which said were containing revelation about “his private phone conversation and financial support his Movement received”.
In an interview with ESAT Radio today, Dr. Berhanu said that such materials were released by the Ethiopian government to divert attention and there was no way that his Movement or himself was going to bicker into an argument of denying or admitting the reports about the said “secret audio”.  However, he stressed that the alleged audio, in which some websites claimed was ‘tapped’ from “his phone conversation”, can be viewed in two ways. He said, the first message that the government wanted to pass was that Ginbot 7 was receiving support from Egypt and that as if his Movement did not value Ethiopia’s national interests. He said “Bereket Simon and his regime can not tell us about the meaning 0f national interest as they don’t know it”.  Secondly, we have always said that we will take any support from anyone for the sake of our struggle for freedom. What we don’t do is that we don’t enter  into any form of  ”negotiation, discussion or agreement in the name of the Ethiopian people and Ethiopia” he affirmed.
This week, some Ethiopian websites carried a story and an audio recording that allegedly stated was a ‘secretly tapped’ audio of the Chairman “talking over the phone about the financial grant he received (from an unnamed source) and how it was being allocated”. The British News International’s phone hacking scandal/journalism has been one of the most scandalous events in the history of journalism in recent times which resulted in the investigation, sacking and arrest of many journalists of the media conglomerate for hacking the telephones of celebrities and politicians to make news.
Dr. Berhanu has neither admitted nor refuted if the said audio was his own voice and phone conversation.

Monday, 17 June 2013

ENTC finalizes preparations for the July consultative conference


June 15, 2013
NEWS RELEASE
ENTC finalizes preparations for the July consultative conference on removing the dictatorship in Ethiopia and replacing it with a transitional government
The Ethiopian National Transitional Council (ENTC) is finalizing preparations for the upcoming all-inclusive consultative conference on removing and replacing the dictatorship in Ethiopia. The conference, which is called to discuss various ideas on how to transition Ethiopia to democracy, will be held on July 2 and 3, in Washington DC. ENTC will also hold its own general assembly on July 4 and 5.Ethiopian National Transitional Council
Delegates from ENTC chapters, representatives from various organizations, invited guests and registered participants will start arriving for the conference on July 1st. (Participation on the conference is by registration and invitation only). Stake holders representing across-section of the Ethiopian people will participate in this important conference and present their ideas on how to form an all-inclusive transitional government after removing the brutal dictatorship in Ethiopia.
ENTC was established in July 2012 with the primary objective of facilitating the formation of a transitional government. Since then, it has been actively organizing its chapters inside Ethiopia and around the world, as well as discussing with the public and organizations about the need for forming a transitional government. ENTC has also been spreading its message inside Ethiopia. ENTC members are currently distributing pamphlets and posters in Ethiopian cities.
Unity is power!
ENTC leadership

Wednesday, 12 June 2013

For how long??????????

By Obang Metho
 
For how long are we Ethiopians going to be oppressed and killed by the same governments that are supposed to protect us? For how long are we going to continue to die on the road as we try to escape from the injustice, misery, pain, death, lack of education and health care as we try to run towards other countries for a better and safer life? We must work together to bring the exodus of our young people to an end!

Ethiopians have to be the ones to find solutions to Ethiopia’s problems. To do so will require that we assume responsibility for breaking down prejudices, apathy, passivity, divisions and dependency. As we do we will be able to achieve far more through cooperation than alone. Strong involvement in our local communities; whether in the Diaspora or within Ethiopia,creates the foundation for representing national interests.

You have a human responsibility to reach out to other Ethiopian people. You have a responsibility to make our beautiful country of Ethiopia, Africa and the world a much better world than it is now and we must do our share!

If there is one thing I would want you to learn from this message it is this--you are not only the child of your family—you are a child of the world and a child of humanity! To the extent that we do this, there is hope! Will you do your part to create a more humane NEW Ethiopia, African and world? That is the world of which I want to be a part. How about you?

May God help us to better love, value and care for our Ethiopian brothers and sisters from every ethnic group throughout our beloved land. Together, may God help us build a bridge to a NEW ETHIOPIA where freedom, peace, justice, equality and respect is shared and enjoyed by all!


Thursday, 6 June 2013

በወይዘሮ አዜብ መስፍን ላይ ምርመራ እንዲደርግ ግፊቱ ጨምራል


ግፊቱ ጨምሯል!!አዜብ መስፍን የሙስና ንግስት ጉድ ፈላባት ዘንድሮ
እነመላኩ ፋንታን ተከትሎ በአዜብ መስፍን ላይ የሚቀርቡ የሙስና አቤቱታዎች ጨምረዋል::
የሙስና ኮሚሽን በአቶ ገብረዋህድ ቤት ባደረገው ፍተሻ እንዲሁም ከኣሁን ቀደም በመርማሪ ደህንነቶች ክትትል በተደረገ የስልክ ጠለፋ የቀድሞ ሟች ጠ/ሚ ባለቤት እና በአለም ትልቁ የሙስና አባት ኤፈርት ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ አዜብ መስፍን ከአቶ ገብረዋህድ ባለቤት እና እህት ጋር በከፍተኛ ደረጃ የቢዝነስ ስራ ይሰሩ እንደነበር እና ከታሰሩት ባለስልጣናት እና ባለሃብቶች ጋር የንግድ አጋርነት እንዳላት አረጋግጧል::ይህንን የሚጠቁሙ ሰነዶች እና ከተለያዩ ወገኖች የሚቀርቡ ጥቆማዎች እና አቤቱታዎች ምርመራው ወደ አዜብ መስፍን አምርቶ ለጥያቄ እንደምትፈለግ ፍንጭ እየሰጠ ነው ሲሉ የሙስና ኮሚጽሽን የውስጥ አዋቂ ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ ተናግረዋል::
ለሙስና ኮሚሽን ከደረሱት አቤቱታዎች ከፊሎቹ :-ኤፈርትን ተገን በማድረግ የተለያዩ እቃዎችን ካለቀረጥ እያስገባች ነው:: ኤፈርት ለመንግስት መክፈል የሚገባውን ህጋዊ የግብርም ሆነ ሌላ ክፍያዎች እንዳይፈጸም አድርጋለች:: ዩዲ ኒሳን ዲዝል ገልባጭ መኪኖችን ካለቀረጥ ነጻ በማስገባት በአቶ ከተማ ከበደ/ኬኬ/ ስም ሸጣለች:: ከዚህ ቀደም እያሱ በርሄ ጋር በኋላም ከኮሎኔል ሃይማኖት ጋር የተከለከሩ የቴለኮሚኒኬሽን ኬብሎችን እና ቴክኖሎጊካል የመገናኛ መሳሪያዎችን ካለቀረጥ በማስገባት ሰርታለች::በነጻ ትሬዲንግ በኩል የተለያዩ ዘመናዊ መኪኖችን ካለቀረጥ እያስገባች በአቶ ነጋ ገ/ዝጌር ስም ትሸጣለች::በሰበታ አለምገና አከባቢ የአበባ ሰፊ እርሻዎች አላት :: በህገወጥ የዶላር እና የኢሮ ዝውውር ውስጥ መሪ ተሳታፊ ናት:: ባንክ ኦፍ ማሌዥያ እና የሲንጋፖር ባልሃብቶችን እንዲሁን ቻይናውያንን በህገወጥ አለማቀፍ የገንዘብ ዝውውር ተባባሪ አድርጋ እየሰራች ነው::በተለያዩ አረብ አገራት እና በሃገር ውስጥ ባስቀመጠቻቸው ደላሎች ኢትዮጵያውያን ሴቶችን በሱዳን እና በየመን አድርጋ ወደ አረብ አገራት ትሸጣለች::በተለያዩ የቤተሰብዋ አባላት ስም ባወጣችው የኮንስትራክሽን ንግድ ፍቃዶች ጨረታዎችን በጉልበት ከመቀማት እየሰራሽ ሲሆን ሌሎች ባለሃብቶችን በስማቸው በመጠቀም የተለያየ ቢዝነሶችን እያካሄደች ነው የሚሉ አቤቱታዎች እና ጥቆማዎች ለሙስና ኮሚሽን የመርማሪዎች ቡድን ደርሷል::
ይህንን ተከትሎ ጠንካራዎቹ የወያኔ አባላት በወይዘሮ አዜብ መስፍን ላይ ምርመራ እንዲደርግ ግፊት እያደረጉ ሲሆን ወይዘሮዋ በአሁን ሰአት ራሳቸውን በተለያየ ምክንያት ገኖ ለማውጣት ላይ ታች እያሉ መሆኑን ታውቋል:

Wednesday, 5 June 2013

“ጦርነት እንኳን ገና በልቶ ላልጠገበ ሕዝብና ለጥጋበኞቹም አይመችም” ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም

ከሰሞኑ መነጋገሪያ እየሆነ የመጣው የግብጽና የኢትዮጵያ በአባይ ጉዳይ እየተሰጣጡ ባለው እሰጥ አገባ ዙሪያ ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም በፌስቡክ ገጻቸው ላይ እንዲህ ብለዋል፦
“ጦርነት እንኳን ገና በልቶ ላልጠገበ ሕዝብና ለጥጋበኞቹም አይመችም፤ የተራበ ሕዝብ በጠገቡ መሪዎች ሲነዳ ግን ጦርነት ለአጉል ጀብደኛነት ዝና የሚጠቅም መስሎ ይታያቸዋል፤ ከኤርትራ ጋር ጦርነት ለመግጠም በሚያሰፈስፉበት ጊዜ በርቱ እያሉ የሚያቅራሩ ሞልተው ነበር፤ ዛሬ አቀራሪዎቹም ሆኑ ጀብደኖቹ በኤርትራ ጦርነት ያለቀባሪስለቀሩት ሰዎች፣ ጠዋሪ ስላጡ እናቶችና አባቶች፣ አሳዳጊ ስለሌላቸው ልጆችና አካለ-ጎደሎ ለሆኑት የሚያስብላቸው አለ ወይ? የአቡነ ጴጥሮስ ሐውልት መነሣትና በኢጣልያ የግራዚያኒ ሐውልት እንዳይሠራ የተጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ ከልክሎ ለሰልፍ የወጡትን አስሮ ያሳደረ አገዛዝ ለአገራቸው ለሞቱት ኢትዮጵያውያን የሚሰጠውን ዋጋ በመጠኑም ቢሆን ያሳያል፤ ስለዚህም ኢትዮጵያውያን አገራቸውን ሲወዱ ራሳቸው በልጽገው ለልጆቻቸው ብልጽግናን እንዲያወርሱ ሕይወታቸውን ቢጠብቁ ለአገራቸውም ክብር ይሆናሉ፡፡
ለፍቅር መተዋወቅ እንደሚያስፈልግ ሁሉ ለጠብም መተዋወቅ ያስፈልጋል፤ የተሟላ መረጃ ቢኖረን የጥንት ታሪክ እየጠቀስን ሰዎችን ለጦርነት እንቀሰቅስም ነበር ብዬ አምናለሁ፤ ስለዚህም አንዳንድ አስፈላጊ መረጃዎችን ላቅርብ፤ —


1. የግብጽ የጦር ኃይል በዓለም አሥረኛ ነው፣ በአፍሪካና በመሀከለኛው ምሥራቅ የሚወዳደረው የለም፤ አንድ ሚልዮን ተኩል ያህል የጦር ኃይል አለው፤ በዓየር ኃይልም ከዓለም አሥራ አራተኛ ነው፤ በታንክ ብዛት አራተኛ ነው፤ በባሕር ኃይል ሰባተኛ ነው፤ በጦር በጀት አርባ ሦስተኛ ነው፤
2. በኢትዮጵያ ዙሪያ ጂቡቲ፣ ሶማልያ፣ ሱዳን የአረብ ማኅበር አባሎች በመሆናቸው ለግብጽ ማኅበረተኞች ናቸው፤ በወያኔ ፈቃድ የተገፋችው ኤርትራም የዚሁ ማኅበር ታዛቢ አባል ነች፤ ከቀይ ባሕር ማዶ ያሉት አገሮች ሁሉ ሀብታሙንና ኃይለኛውን ሳኡዲ አረብያንም ጨምሮ የግብጽ ማኅበርተኞች ናቸው፤ በዚህ ሁሉ መሀከል የተከታተፈች ኢትዮጵያ ብቻዋን ነች፤
3. የቤንዚን ሀብትና ከሀብቱም ጋር የሚገኘውን ወዳጅና ጡንቻ አንርሳ፤
ይህ ማስታወሻ ለማስፈራራት አይደለም፤ ማስፈራራትን አላውቅበትም፤ እንዲያውም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ‹‹አትፍሩ›› ብሏቸዋል ተብዬ ተከስሼ ታስሬአለሁ፤ ስለዚህ አላስፈራራም፤ ጦርነት ከመጣብን ልናስቀረው እንሞክር፤ ሌላው ቢቀር እንድንዘጋጅ ጊዜ እናገኛለን፤ ገፍቶ ከመጣ ግን እንቋቋመዋለን፤ ለጦርነት አንቸኩል፤ ለኤርትራም ጊዜ ተናግሬ ነበር፤ የሰማኝ የለም፤ ጥጋብ ላይ ያሉ የሚርባቸው ዝና ነው፤ የሚያገኙት ግን ውርደትን ነው፡፡

Monday, 3 June 2013

አዲስ ፍጥጫ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ




በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ውስጥ የፖለቲካ ፍጥጫ እና የስልጣን ሽኩቻ እየታየ መሆኑን መረጃዎች ጠቁመዋል:: በሁለት ወገን በሕቡእ እንደተሰለፉ የሚታሙት እንዲሁም ለሕወሓት መረጃ ያቀብላሉ በሚባሉ አመራሮች መካከል ከፍተኛ የሆነ የፖለቲካ ግብግብ መፈጠሩን የውስጥ አዋቂ ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ ጠቁመዋል::
ምንጮቹ እንደጠቆሙት ከሆን በረከት ስምኦን የራሱን ቡድን አደራጅቶ ሕወሃቶችን በማለሳለስ ሃይለማርያምን እየመራው እንደሚገኝ የገለጡ ሲሆን ለላኛው ቡድን ደሞ ለሃይለማርያም ድፍረት ለመስጠት እየሰራ የሚገኝ እና የሕወሃት ደህንነቶችን በጥገኝነት የተጠጋ መሆኑን ገልጸዋል::
በረከት ስምኦን በተለያዩ ጊዜያት ከሃይለማርያም ጋር ስምምነት እንዳሌለው ያዩ እና በመካከላቸው አለመግባባት መኖሩን የተመለከቱ የወያኔ የበላይ አመራሮች እስከመቼ ተመሪ ሆነህ ትቀጥላልህ በማለት ሃይለማርያምን የሚያደፋፍሩ ሲሆን በተዘዋዋሪ ባለቤታቸው ወይዘሮ ሮማንን ባልሽ እንዲደፍር አበረታችው በማለት የሚጠዘጥዙ ወገኖች እንደተፈጠሩ ምንጮቹ አክለው አስረድተዋል::
በረከት የራሱን ርእዮት አለም የሚደግፉለትን  ከተለያዩ ክልሎች ያሉ የኢህኣዴግ ካድሬዎችን በማደራጀት ላይ ሲሆን ብኣዴንን በተመለከተ ምንም የሚሰራው ድርጅታዊ ስራ እንደሌለ የተጠቆመ ሲሆን ከስልጣኑ ውጭ የሆኑ ስራዎችን ለመስራት በተለያየ ጊዜ የሞከራቸው ሙከራዎች በአቶ ሃይለማርያም የተደናቀፉ መሆኑን እና ከተደናቀፉ ጉዳዮችም አንዱ ኤርትራውያንን በወያኔ ስር የማደራጀት እንዲሁም ኢትዮጵያዊ ዜግነት የመስጠት በማለት ወደ ወያኔ/ኢህኣዴግ ይበልጥ ሰርገው እንዲገቡ ለመመልመል ያደረገው ሙከራ እና ቀጣዩን የወያኔ የስልጣን ርክክብ ለእነዚህ ላሰባቸው የኤርትራውያን ህዋሶች ለመስጠት ያሰበው ተደናቅፎበታል::
ይህንን እና ሌሎች ጉዳዮችን ተከትሎ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ አከባቢ ፍጥጫ መኖሩን እና እንዳይካረር ያሰጋል ሲሉ ምንጮቹ ለምንሊክ ሳልሳዊ ጠቁመዋል::